• የመስከረም 8 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
    Sep 18 2024
    በደቡብ ምዕራብ ዳርፉር ውስጥ የሱዳን ጦር ባካሄደው የአየር ጥቃት ከ40 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተነገረ። ዩናይትድ ስቴትስ የሱዳን ተቀናቃኝ ኃይሎች በአስቸኳይ ለውይይትም እንዲቀመጡ ጠይቃለች። የዩናይትድ ስቴትስ ሰው አልባ አውሮፕላን የመን አቅራቢያ መከስከሱን ፔንታገን አረጋገጠ። የየመን ሁቲ ሚሊሺያዎች ባለፉት ቀናት በርካታ አውሮፕላኖችን መትተው መጣላቸውን አስታውቀው ነበር። ሊባኖስ ውስጥ በድምፅና መልእክት መቀበያ መሣሪያ ፍንዳታ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ማሻቀቡ እየተነገረ ነው። ማዕከላዊ አውሮጳን ከሁለት አስርት ዓመታት ወዲህ ያጥለቀለቀው አስከፊ የጎርፍ አደጋ ከሮማንያ እስከ ፖላንድ ከባድ ውድመት አስከትሏል።
    Show more Show less
    10 mins
  • የዓለም ዜና፤ መስከረም 7 ቀን፤ 2017 ዓ.ም ሰኞ
    Sep 17 2024
    DW Amharic የካይሮ መንግሥት ህወሓት እና ኤርትራን ማደራደር እንደሚፈልግ ተመለከተ። ግብፅና ኤርትራ ትስስራቸዉን ለማጠናከር ወታደራዊ ትብብር እና የመረጃ ልውውጥ ስምምነት ሊፈፅሙ እንደሚችል የግብፅ የዜና ምንጮች ዘገቡ። በጎንደር ከተማ ዛሬ ከማለዳ ጀምሮ በፋኖና በመንግስት ወታደሮች መካከል ውጊያ ሲካሄድ መዋሉን ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል ቱርክ አንካራ ላይ ሊደረግ የታቀደው ሦስተኛ ዙር ዉይይት ለሌላ ጊዜ መተላለፉን የሶማልያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ተናገሩ። ደቡብ ሱዳን በጎረቤቷ ሱዳን በኩል ወደ ውጭ ሃገር የነዳጅ ምርትን ለመላክ እና እንደገና ለማስጀመር እየሰራች መሆኑ ተነገረ።
    Show more Show less
    11 mins
  • DW Amharic የመስከረም 6 ቀን 2017 የዓለም ዜና
    Sep 16 2024
    አዲሱ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ 16 የቀድሞ ከፍተኛ አመራሮች ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማገዱ አስታወቀ። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ብልጽግና ፓርቲ አባላቱን ሲያሰለጥን እንዳለፈው ዓመት “ከመንግሥት ካዝና ገንዘብ አውጥቶ” እየከፈለ ነው ሲል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ወነጀለ።የኬንያ ዋና ኦዲተር ሀገሪቱ ከተለያዩ ወገኖች የተበደረችውን ዕዳ ኦዲት ማድረግ መጀመሩን የፋይናንስ ሚኒስትሩ ተናገሩ። በምዕራብ እና ማዕከላዊ አፍሪካ በጣለ ከባድ ዝናብ እና ባስከተለው ጎርፍ ምክንያት ከ500 በላይ ሰዎች ሕይወታቸውን እንዳጡ የተመ አስታወቀ።
    Show more Show less
    10 mins
  • የመከረም 5 ቀን 2017 የዓለም ዜና
    9 mins
  • የመስከረም 4 ቀን 2017 ዓ/ም የዓለም ዜና
    10 mins
  • የዓርብ መስከረም 3 ቀን 2016 ዓ/ም የዓለም ዜና
    Sep 13 2024
    DW Amharic-በኮሬ ዞን በእገታ ላይ የነበሩ አራት አርሶ አደሮች መገደላቸው፤በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን አንድ ድልድይ በመደርመሱ፤ ዞኑን ከአጎራባች አካባቢዎች ጋር የሚያገናኝ መንገድ አገልግሎት እንደማይሰጥ መገለፁ፤የሴኔጋሉ ፕሬዝዳንት የሀገራቸውን ፓርላማ መበተናቸው፤መካከለኛው አውሮፓ በመጭው ቅዳሜና እሁድ በሚጥለው ከባድ ዝናብ ለከፍተኛ የጎርፍ ይጋለጣል መባሉ፤የሰሜን ኮሪያው መሪ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ የኒውክሌር ማብላያ እና የዩራኒየም ማበልፀጊያ ቦታዎችን መጎብኘታቸው፤ዶናልድ ትራምፕ ከተፎካካሪያቸው ካማላ ሀርስ ጋር ሌላ የምርጫ ክርክር እንደማያደርጉ ማስታወቃቸው የዛሬው የዓለም ዜና ያካተታቸው ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው።
    Show more Show less
    11 mins
  • የመስከረም 2 ቀን ፣ 2017 ዓ.ም.የዓለም ዜና
    Sep 12 2024
    የሐሙስ መስከረም 2 ቀን 2017 ዓም አርዕስተ ዜና የተባበሩት መንግሥታት የትምሕርት የሳይንስና የባህል ድርጅት በምህጻሩ ዩኔስኮ ዩኔስኮ የሱዳን ብሔራዊ ቤተ መዘክርን ጨምሮ በሌሎች የሱዳን ቤተ መዘክሮች እና የቅርስ ተቋማት ላይ ተፈጽመዋል የሚባሉ ዝርፊያዎችና ጉዳቶች በእጅጉ አሳስቦኛል አለ። ስዊድን ወደ ሀገራቸው በፈቃደኝነት ለሚመለሱ ስደተኞች እስከ 34 ሺህ ዶላር እንደምትከፍል አስታወቀች። በደቡብ ምዕራብ እስያን የመታው ያጊ የተባለው ወጀብ ያስከተለው ጎርፍ የገደለው ሰው ቁጥር ከ250 በለጠ።
    Show more Show less
    11 mins
  • የረቡዕ መስከረም 1 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
    10 mins