• የዓለም ዜና

  • By: DW
  • Podcast

የዓለም ዜና

By: DW
  • Summary

  • ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።
    2024 DW
    Show more Show less
Episodes
  • የመስከረም 8 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
    Sep 18 2024
    በደቡብ ምዕራብ ዳርፉር ውስጥ የሱዳን ጦር ባካሄደው የአየር ጥቃት ከ40 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተነገረ። ዩናይትድ ስቴትስ የሱዳን ተቀናቃኝ ኃይሎች በአስቸኳይ ለውይይትም እንዲቀመጡ ጠይቃለች። የዩናይትድ ስቴትስ ሰው አልባ አውሮፕላን የመን አቅራቢያ መከስከሱን ፔንታገን አረጋገጠ። የየመን ሁቲ ሚሊሺያዎች ባለፉት ቀናት በርካታ አውሮፕላኖችን መትተው መጣላቸውን አስታውቀው ነበር። ሊባኖስ ውስጥ በድምፅና መልእክት መቀበያ መሣሪያ ፍንዳታ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ማሻቀቡ እየተነገረ ነው። ማዕከላዊ አውሮጳን ከሁለት አስርት ዓመታት ወዲህ ያጥለቀለቀው አስከፊ የጎርፍ አደጋ ከሮማንያ እስከ ፖላንድ ከባድ ውድመት አስከትሏል።
    Show more Show less
    10 mins
  • የዓለም ዜና፤ መስከረም 7 ቀን፤ 2017 ዓ.ም ሰኞ
    Sep 17 2024
    DW Amharic የካይሮ መንግሥት ህወሓት እና ኤርትራን ማደራደር እንደሚፈልግ ተመለከተ። ግብፅና ኤርትራ ትስስራቸዉን ለማጠናከር ወታደራዊ ትብብር እና የመረጃ ልውውጥ ስምምነት ሊፈፅሙ እንደሚችል የግብፅ የዜና ምንጮች ዘገቡ። በጎንደር ከተማ ዛሬ ከማለዳ ጀምሮ በፋኖና በመንግስት ወታደሮች መካከል ውጊያ ሲካሄድ መዋሉን ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል ቱርክ አንካራ ላይ ሊደረግ የታቀደው ሦስተኛ ዙር ዉይይት ለሌላ ጊዜ መተላለፉን የሶማልያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ተናገሩ። ደቡብ ሱዳን በጎረቤቷ ሱዳን በኩል ወደ ውጭ ሃገር የነዳጅ ምርትን ለመላክ እና እንደገና ለማስጀመር እየሰራች መሆኑ ተነገረ።
    Show more Show less
    11 mins
  • DW Amharic የመስከረም 6 ቀን 2017 የዓለም ዜና
    Sep 16 2024
    አዲሱ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ 16 የቀድሞ ከፍተኛ አመራሮች ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማገዱ አስታወቀ። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ብልጽግና ፓርቲ አባላቱን ሲያሰለጥን እንዳለፈው ዓመት “ከመንግሥት ካዝና ገንዘብ አውጥቶ” እየከፈለ ነው ሲል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ወነጀለ።የኬንያ ዋና ኦዲተር ሀገሪቱ ከተለያዩ ወገኖች የተበደረችውን ዕዳ ኦዲት ማድረግ መጀመሩን የፋይናንስ ሚኒስትሩ ተናገሩ። በምዕራብ እና ማዕከላዊ አፍሪካ በጣለ ከባድ ዝናብ እና ባስከተለው ጎርፍ ምክንያት ከ500 በላይ ሰዎች ሕይወታቸውን እንዳጡ የተመ አስታወቀ።
    Show more Show less
    10 mins

What listeners say about የዓለም ዜና

Average customer ratings

Reviews - Please select the tabs below to change the source of reviews.